Psalms 3

የመከራ ተቀባዩ የጧት ጸሎት

ዳዊት ከልጁ ከአቤሴሎም በሸሸ ጊዜ የዘመረው መዝሙር።

1 እግዚአብሔር ሆይ፤ ጠላቶቼ ምንኛ በዙ!
ስንቱስ በእኔ ላይ ተነሣ!
2ብዙዎች ነፍሴን፣ “እግዚአብሔር
አይታደግሽም” አሏት። ሴላ
በመዝሙረ ዳዊት ውስጥ በተደጋጋሚ የሚገኝ ሲሆን፣ የቃሉ ትርጕም በትክክል አይታወቅም፤ የሙዚቃ ምልክት ሳይሆን አይቀርም


3 እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ ግን ዙሪያዬን
የምትከልል ጋሻ ነህ፤
ክብሬንና ራሴንም ቀና ቀና
የምታደርግ አንተ ነህ።
ወይም እግዚአብሔር… ወደ ላይ የምታነሣ ክብሬ ሆይ

4ወደ እግዚአብሔር ድምፄን ከፍ አድርጌ እጮሃለሁ፤
እርሱም ከተቀደሰ ተራራው ይመልስልኛል። ሴላ

5እተኛለሁ፤ አንቀላፋለሁ፤
እግዚአብሔር ደግፎ ይዞኛልና እነቃለሁ።
6በየአቅጣጫው የከበበኝን፣
አእላፍ ሕዝብ አልፈራም።

7 እግዚአብሔር ሆይ ተነሥ!
አምላኬ ሆይ፤ ታደገኝ፤
የጠላቶቼን ሁሉ መንጋጋ ትመታለህ፤
የክፉዎችንም ጥርስ ትሰባብራለህ።

8ማዳን የእግዚአብሔር ነው፤
በረከትህ በሕዝብህ ላይ ይሁን። ሴላ
Copyright information for AmhNASV